ፈልግ

Cookie Policy
The portal Vatican News uses technical or similar cookies to make navigation easier and guarantee the use of the services. Furthermore, technical and analysis cookies from third parties may be used. If you want to know more click here. By closing this banner you consent to the use of cookies.
I AGREE
ኒቆዲሞስ ከኢየሱስ ጋር በመገናኘቱ ተስፋውን መልሶ አገኘ ኒቆዲሞስ ከኢየሱስ ጋር በመገናኘቱ ተስፋውን መልሶ አገኘ 

ኒቆዲሞስ ከኢየሱስ ጋር በመገናኘቱ ተስፋውን መልሶ አገኘ

ኢየሱስን በሌሊት ሊጠይቀው ወደ እርሱ በመጣ ጊዜ ኒቆዲሞስ “ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ከመንፈስ የተወለደ መንፈስ ነው" እያለ ተናገረው (ዮሐንስ 3፡6) ምን ማለቱ ነው? አንተ እኔን ፈልገህ መጣህ፡፡ ግን እወቅ አንተ ሥጋዊ ነህ፣ ከሥጋ ስለተወለድክ እኔ ግን መንፈሳዊ ነኝ፣ ከእግዚአብሔር የመንፈስ የመጣሁ በመሆኔ መንፈሳዊና ሥጋዊ ደግሞ አይስማሙም፣ ስለዚህ የእኔ መሆን ከፈለግህ ሥጋዊ መሆኑን ትተህ መንፈሳዊ መሆን አለብህ መንፈስን ልትለብስ ይገባሃል፡፡ አለበለዚያ አንስማማም ለየብቻችን ነንና የእኔ መሆን አትችልም ማለቱ ነው።

ሀ/ ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው ማለት ምድራዊ ጊዜያዊ ሰው ነው። ሥጋዊ ሰው በሥጋ መንገድ ይሄዳል፣ ሥጋዊ ነገር ያስባል፣ ይፈልጋልም ስለ ሥጋው ይኖራል፣ ይሠራልም “ሥጋቸውን የሚያገለግሉ ዓለማዊ ናቸው" (ሮሜ 8፣5) ይለናል ቅዱስ ጳውሎስ። ሥጋዊ ሰው የዓለም ልጅ በመሆኑ የዓለምን መንፈስ ይከተላል፤ የእግዚአብሔር ፍርሃትና የነፍሱ ደኀንነት ሐሳብ የለውም፣ የመንፈስ ነገር አይባውም፣ ይህ ለእርሱ ሞኝነት ነው" ይላል (1ኛ ቆሮ. 2፣14)።

ለ/ ከመንፈስ የተወለደ መንፈስ ነው፥ ሰማያዊና ዘለዓለማዊ መልአክ የእግዚብሔር ልጅ ነው፣ ይህ ሰው በእግዚአብሔር መንፈስ ስለሚመራ ሰማያዊ ነገርን ይመኛል። አእምሮው ልቡ ፍላጐቱ ወደ አምላክ ያዘነብላል። ከመንፈስ የተወለደ ሰው ስለ አምላክ ክብርና ደኀንነት ባለው ኃይል ሁሉ ይታገላል፣ ከሁሉ አስቀድሞ የሚገደው የእግዚአብሔርና የነፍሱ ነው እንጂ የዓለምን ነገር አይደለም። የእግዚአብሔርን መንፈስ የለበሰ የዓለም መንፈስ ይጠላል፣ ከእርሱ ይሸሻል፣ ከኃጢአት ይርቃል። ከመንፈስ የተወለደ መንፈስ በመሆኑ የብርሃን የጽድቅ ልጅ ነው፣ የሥጋ ልጆችና የመንፈስ ልጆች አይስማሙም ሐሳባቸው የተለያየ ነው። “ሥጋ የኃጢአትን ሕግ ያገለግላል፣ ተቃራኒ መንፈስ ደግሞ ይፈልጋል። መንፈስ ደግሞ ተቃራኒ የሥጋ አንጻር ይፈልጋል፣ እርስ በርሳቸው ይዋጋሉ" (ገላ. 5፣17) ይላል ቅዱስ ጳውሎስ የሥጋ መንገድ የጥፋት መንገድ ነው፣ የመንፈስ መንገድ ግን የጽድቅ መንገድ ነው፡፡

የኢየሱስ ተከታዮች መሆንን አንተው የመንፈስ ልጆች እንሁን፣ የሥጋ ግብርን ፍላጐትን እንተው፣ ሥጋችንን እናሸንፍ፣ ዓለምን ደግሞ እንናቅ፣ እንመንን በመንፈስ እንደገና እንድንወለድ በክርስቶስ መንፈስ መኖር ያስፈልገናል። ያደረግነውን ብናደርግ፣ ብንከተል ድርጊታችንን እንመስላለን፣ የእርሱ ተከታዮች እንሆናለን።

 

20 Mar 2025, 14:14
Prev
April 2025
SuMoTuWeThFrSa
  12345
6789101112
13141516171819
20212223242526
27282930   
Next
May 2025
SuMoTuWeThFrSa
    123
45678910
11121314151617
18192021222324
25262728293031