ፈልግ

Cookie Policy
The portal Vatican News uses technical or similar cookies to make navigation easier and guarantee the use of the services. Furthermore, technical and analysis cookies from third parties may be used. If you want to know more click here. By closing this banner you consent to the use of cookies.
I AGREE
የጀርመን ፍራንችስካዊያን የወንጌል ተልዕኮ እንቅስቃሴ አባላትን ተቀብለው ባነጋገሩበ ጊዜ፣ የጀርመን ፍራንችስካዊያን የወንጌል ተልዕኮ እንቅስቃሴ አባላትን ተቀብለው ባነጋገሩበ ጊዜ፣ 

ር. ሊ. ጳ. ፍራንችስኮስ “ቤተክርስቲያን እውነተኛ ለውጥን ማምጣት የምትችለው የእግዚአብሔርን ቃል በማዳመጥ ብቻ ነው”።

ከእግዚአብሔር ዘንድ ቅዱስ ፍራንችስኮስን የደረሰው ጥሪ ቤተክርስቲያኑን እንዲያድስ የሚል እንደነበር ያስታወሱት ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ፣ ቅዱስ ፍራንችስኮስ በዘመኑ የቤተክርስቲያን አቅም ውስን መሆኑን ቢገነዘብም ቅድሚያን የሰጠው እውነተኛ የወንጌል ሕይወትን እንደመረጠ ገልጸዋል ።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ ዮሐንስ መኰንን - ቫቲካን

የአሲዚው ቅዱስ ፍራንችስኮስ በዘመኑ ከሁሉም በላይ ወንጌልን በተግባር መኖር የቻለ መሆኑን ያስታወሱት ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ፣ ቤተክርስቲያን እውነተኛ ለውጥን ማምጣት የምትችለው እግዚአብሔርን ብቻ በማዳመጥ እንደሆነ አስገንዝበዋል። ቅዱስነታቸው ይህን ያስታወቁት ቅዳሜ ጠዋት መጋቢት 28 ቀን 2011 በቫቲካን ውስጥ የርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ለተቀበሏቸው ፍራንቸስካዊያን ገዳማዊያት እና ገዳማዊያን እንዲሁም ምዕመናን ባሰሙት ንግግር ነው። የፍራንችስካዊ ተልዕኮ እንቅስቃሴ የተመሠረተበትን 50ኛ ዓመት ለማክበር ከጀርመን ወደ ሮም የመጡት በቁጥር 25 የሚሆኑ የእንቅስቃሴው አባላት ለቅዱስነታቸው ሰላምታቸውን አቅርበውላቸዋል።  

ተልዕኮአችሁ ድሆችን እና ስደተኞችን ማገዝ ይሁን፣

ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ፣ በጀርመን ቦን ከተማ አቅራቢያ ፍራንችስካዊያኑ በማበርከት ላይ ለሚገኙት አገልግሎት አድናቆታቸውን ገልጸዋል። ቅዱስነታቸው በንግግራቸው እንደገለጹት ገዳሚያዊያን እና ገዳማዊያት ከምዕመናን ጋር በመተጋገዝ፣ ሌሎች ምእመናኖችም እንዲተባበሩ በማድረግ፣ በመላው ዓለም የሚገኙ የደሄዩት እና የተሰደዱት የወደ ፊት መልካም ተስፋ እንዲኖራቸው ለማድረግ የምታደርጉት ጥረት መልካም ነው ብለዋል።

የቅዱስ ፍራንችስኮስ ምሳሌ ሕያው ነው፣

ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌሉ “ከእነዚህ ወንድሞች መካከል ለአንዱ ያደረጋችሁት ለእኔ እንዳደርጋችሁ ነው” ያለውን ያስታወሱ ቅዱስነታቸው፣ ፍራንችስካዊ ልኡካን ማሕበር የሚከተለው መንገድ ቅዱስ ፍራንችስኮስ የመረጠው የድህነት ሕይወት እና ከደሆች ጋር በመሆን ሕይወቱን በሙሉ ለኢየሱስ ክርስቶስ አደራ በመስጠት ደስታ እና የእርሱን በረከት ያገኘበት መንገድ መሆኑን አስረድተዋል። የማዕከላቸው ዓላማ ይህ በመሆኑ በመላው ዓለም ውስጥ የቸርነት፣ የአንድነት እና የወንድማማችነት መንፈስ እንዲስፋፋ ማድረጋቸውን አስታውሰዋል።

ቤተክርስቲያን አቅሟ ውስን ቢሆንም የእግዚአብሔርን ጥሪ ማዳመጥ ያስፈልጋል፣

ከእግዚአብሔር ዘንድ ቅዱስ ፍራንችስኮስን የደረሰው ጥሪ ቤተክርስቲያኑን እንዲያድስ የሚል እንደነበር ያስታወሱት ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ፣ ቅዱስ ፍራንችስኮስ በዘመኑ የቤተክርስቲያን አቅም ውስን መሆኑን ቢገነዘብም ቅድሚያን የሰጠው እውነተኛ የወንጌል ሕይወት መኖር እንደነበር አስታውሰዋል። ዛሬም ቢሆን ቤተክርስቲያን የአቅም ውስንነት እንደሚታይባት ገልጸው በመስቀል ላይ የተሰቀለው ኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያኑ እንድንደግፍ እና እንድናሳድግ ለእያንዳንዳችን ጥሪውን ያቀርብልናል ብለዋል። በቤተክርስቲያን ለውጥ ሊመጣ የሚችለው እርሱን በማዳመጥ፣ ሁሉን ለእርሱ አሳልፎ በመስጠት እና በመልካም ሥራዎቻችን ከእርሱ ጋር ስንተባበር ነው ብለዋል።

ዛሬ በሚያጋጥሙን ችግሮች ሳንሸነፍ ከወትሮ በበለጠ ራሳችንን ለአገልግሎት በማነሳሳት መጪው ጊዜ መልካም እንዲሆን ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።  ዛሬ በሚያጋጥሙን ችግሮች ሳንሸነፍ ከወትሮ በበለጠ ራሳችንን ለአገልግሎት በማነሳሳት መጪው ጊዜ መልካም እንዲሆን ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል። የፍራንችስካዊያኑ የወንጌል ተልዕኮ ማዕከልም በተግባር እየገለጸ ባለው የሕይወት ምስክርነት ብዙ አስተዋጽኦን ሊያበረክት ይችላል ብለዋል። ቅዱስነታቸው በመጨረሻም አባላቱ አገልግሎታቸውን የጋራ ጥቅምን እና የተፈጥሮ ደህንነትን ባገናዘበ መልኩ እንዲያከናውኑ አሳስበዋል።

ይህን ዘገባ በድምጽ ለማዳመጥ ከዚህ ቀጥሎ የሚገኘውን “ተጫወት” የሚለውን ምልክት ይጫኑ!
08 Apr 2019, 17:05
Prev
March 2025
SuMoTuWeThFrSa
      1
2345678
9101112131415
16171819202122
23242526272829
3031     
Next
April 2025
SuMoTuWeThFrSa
  12345
6789101112
13141516171819
20212223242526
27282930