ፈልግ

Cookie Policy
The portal Vatican News uses technical or similar cookies to make navigation easier and guarantee the use of the services. Furthermore, technical and analysis cookies from third parties may be used. If you want to know more click here. By closing this banner you consent to the use of cookies.
I AGREE

ር. ሊ. ጳ ፍራንችስኮስ በስሎቫኪያ ሐዋርያዊ ጉብኝት እንደሚያደርጉ አስታወቁ

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ ዮሐንስ መኰንን - ቫቲካን

ር. ሊ. ጳ ፍራንችስኮስ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ከመስከረም 2 - 5/2014 ዓ. ም ድረስ በስሎቫኪያ ሐዋርያዊ ጉብኝት የሚያደርጉ መሆኑን አስታውቀዋል። ይህን ዜና ባበሰሩ ጊዜ በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ የተሰበሰቡት የስሎቫኪያ ምዕመናን ደስታቸውን በጭብጨባ ሲገልጹ ታይተዋል። እሑድ መስከረም 2/2014 ዓ. ም ጠዋት ላይ በሃንጋሪ ዋና ከተማ ቡዳፔስት ሲካሄድ የቆየው ዓለም አቀፍ የቅዱስ ቁርባን ጉባኤ ማጠቃለያ መስዋዕተ ቅዳሴ ጸሎትን የሚመሩ መሆኑን ገልጸዋል። ወደ ስሎቫኪያ የሚያደርጉት ሐዋርያዊ ጉብኝት በመልካም እንዲፈጸም ምዕመናን በጸሎታቸው እንዲያግዟቸው ጠይቀው፣ ለሐዋርያዊ ጉብኝታቸው መሳካት ሰፊ ዝግጅት እና የበኩላቸውን ጥረት በማድረግ ላይ ለሚገኙት በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበውላቸዋል።

ርዕሠ ሊቃነ ፍራንችስኮስ ቀጥለውም ከሮም ከተማ፣ በጣሊያን ውስጥ ከተለያዩ ሀገረ ስብከቶች ለመጡት ምዕመናን፣ ለውጭ አገራት መንፈሳዊ ነጋዲያን እና ሀገር ጎብኚዎች ሰላምታቸውን አቅርበውላቸዋል። በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለተገኙት የስሎቫኪያ ምዕመናን እና በአደባባዩ ለተገኙት በሙሉ ሰላምታቸውን አቅርበው መልካም ዕለተ ሰንበትን ከተመኙላቸው በኋላ ምዕመናኑ በጸሎታቸው እንዲያስታውሷቸው አደራ ብለዋል።

05 Jul 2021, 20:15
Prev
March 2025
SuMoTuWeThFrSa
      1
2345678
9101112131415
16171819202122
23242526272829
3031     
Next
April 2025
SuMoTuWeThFrSa
  12345
6789101112
13141516171819
20212223242526
27282930