ፈልግ

ቬኒስ ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስን በደስታ ተቀብላ ማስተናገዷ ተገለጸ!

የጣሊያኗ ቬኒስ ከተማ እሁድ ሚያዝያ 20/2016 ዓ.ም ጧት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስን መቀበሏ የተገለጸ ሲሆን የቫቲካን ዜና ወኪላችን ዲቦራ ካስቴላኖ ሉቦቭ፣ ከቬኒስ አርት ቢያናሌ ጎን የርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳቱን የሐዋርያዊ ጉብኝት መርሐ ግብር እንደሚከተለው አስቃኝታናለች።

የእዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ ቫቲካን

ጎንዶላ በመባል የሚታወቁ ጥንታዊ ጀልባዎች እና ግርማ ሞገስ የተላበሱ ቦዮች ምስሎችን የሚቀሰቅሱትን በዓለም አቀፍ ደረጃ በጣም ከሚወዷቸው እና ታዋቂ ከሆኑ ከተሞች አንዷ የሆነችው ቬኒስ፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ አጭር ግን ጠንካራ የአንድ ቀን ሐዋርያዊ ጉብኝት አድርገዋል።

ብዙ አለም አቀፍ ቱሪስቶችን የሳበችውን የጣሊያኗን ከተማ የመጀመርያውን የጳጳሱ ጉብኝት የሚያመላክት ሲሆን በዚህ ሳምንት ብቻ መጨናነቅን ለመግታት በአለም የመጀመሪያውን የቱሪስት መግቢያ ክፍያ 5 ዩሮ ማስተዋወቅ ነበረባት ከተማዋ።

ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ወደ እዚያው ያቀኑት በሄሊኮፕተር እንደ ነበረ የተገለጸ ሲሆን በጀልባ እየተዘዋወሩ ከዓመቱ መጀመሪያ ጀምሮ ከሮም ውጭ የሚያደርጉትን የመጀመሪያ ጉብኝታቸውን አከናውነዋል።    ይህም በቀጣዮቹ 3 ወራት በጣሊያን ካቀዷቸው በርካታ የሐዋርያዊ ጉብኝቶች የመጀመሪያው ነው። በመስከረም ወር በመላው እስያ እና ኦሺኒያ የአራት ሀገራት ሐዋርያዊ ጉዞ የሚያካሂዱበት የቅዱስ አባታችን ረጅሙ ጉብኝት ቀደም ብሎ ተገልጿል።

ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ የጳጳሳት መኖሪያ

በ20ኛው ክፍለ ዘመን ሶስት የቬኒስ ፓትርያርኮች ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሆነው የተመረጡባት ይህች ከተማ፣ ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ “የእንኳን ደህና መጣችሁ” አቀባበል የተደርገላቸው ሲሆን ይህም ጳጳስ የቬኒስ አርት ቢሊየንያን ሲጎበኟቸው ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑ ነው። የሁለት ዓመት በዓል እ.አ.አ በ1895 የጀመረ ሲሆን ዘንድሮ ደግሞ 60 ዙር ላይ ደርሷል።  በታላቁ ዓለም አቀፍ የኪነ ጥበብ ዝግጅት ላይ የቅድስት መንበር ተሳትፎ እ.አ.አ ከ2013 ዓ.ም. በኋላ እየጎላ መጥቷል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ ጁዴካ በመባል የሚታወቀውን የሴቶች እስር ቤት እንደ ጎበኙ የተገለጸ ሲሆን፣ ይህም “በራሴ አይን” የሚል ርዕስ ያለው እና በኅብረተሰቡ ተገልለው ለሚኖሩ የሰብአዊ መብቶች እና ሰዎች መሪ ቃል ነው።

በሐይቅ ከተማ ውስጥ ሙሉ አጀንዳ

በእስር ቤቱ ውስጥ ለሚገኙ የሕግ ታራሚዎች ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ ሰላምታ እንዳቀረቡ የተገለጸ ሲሆን የሕግ ታራሚዎችን በተናጠል አነጋግረዋል፣ ይህ ቅጽበት ጳጳሱ ከሴት እስረኞች ጋር ያሳለፉትን የጥራት ጊዜ ትዝታ እንደሚያስታውስ እርግጠኛ ይሆናል፣ ከአንድ ወር ባነሰ ጊዜ ውስጥ፣ የጎርጎሮሳዊያኑን የቀን አቆጣጠር በሚከተሉ የክርስቲያን ማሕበረሰቦች ዘንድ ተከብሮ ያለፈውን የጸሎተ ሐሙስ እለት ምክንያት በማድረግ በሮም ከተማ ውስጥ በሚገኘው ማረሚያ ቤት ውስጥ የሚገኙትን የሕግ ታራሚዎችን እግራቸውን በማጠብ፣ በእዚያ የተካሄደውን ሥርዓተ አምልኮ መምራታቸው ይታወሳል።

በመቀጠልም ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ በሲስቲን ቻፕል ውስጥ ለአርቲስቶች ንግግር ካደረጉ ከአንድ ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ በእስር ቤቱ የጸሎት ቤት ውስጥ ብዙዎች ከፓቪልዮን ጋር ከተያያዙ አርቲስቶች ጋር የተገናኙ ሲሆን ከዚያም ከቬኒስ እና ከቬኔቶ ወጣቶች ጋር ተገናኝተዋል፣ ይህ ጊዜ ትዝታዎችን የሚያነቃቃ ጊዜ ነበር። ባለፈው ነሐሴ ወር በሊዝበን ፖርቱጋል በተካሄደው የዓለም ወጣቶች ቀን ጳጳሱ ከወጣቶች ጋር ያደረጉት ንግግር በድጋሚ አስታውሰዋል።

በመቀጠልም ቅዱስ አባታችን በጀልባዎች ላይ በተሠራው ጊዜያዊ ድልድይ ወደ ቅዱስ ማርቆስ አደባባይ በማምራት መስዋዕተ ቅዳሴ ማሳረጋቸው የተገለጸ ሲሆን ከፋሲካ በዓል በኋላ የሚደገመውን “የሰላም ንግሥት ሆይ ደስ ይበልሽ፣ እንደ ተናገረው ከሙታን ተነስቷልና” የተሰኘውን ጸሎት ከምዕመናኑ ጋር ደግመዋል፣ ወደ ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን በመግባት የቅዱሳኑን ንዋየ ቅድሳትን ተመልክተዋል።

ፈለግ በመከተል ላይ

በቅዱስ ማርቆስ አደባባይ በተለይ ደስታው ጎልቶ የታየ ሲሆን በርካታ መዘምራን እና የባሕል ሙዚቀኞች ለቅዱስነታቸው አቀባበል ማድረጋቸው ተገልጿል። ቅዱስነታቸው በርካታ ምዕመናን እና የአገር ጎቢኚዎች በተገኙበት መስዋዕተ ቅዳሴ ማሳረጋቸው ተገልጿል። በርካታ የቅርብ ጊዜ ሊቃነ ጳጳሳት ቬኒስን ሲጎበኙ፣ ከተማዋ እ.አ.አ በ2011 ዓ.ም በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በነዲክቶስ 16ኛ የተጎበኘች አገር ስትሆን ከተማዋ ይህንን እና እያንዳንዱን የጳጳስ ጉብኝት እንደ ታሪካዊ እና ልዩ ጊዜ ትመለከታለች፣ እናም በ1985 ዓ.ም የርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ቅዱስ ዮሐንስ ጳውሎስ 2ኛ የተደረገውን ጉብኝት፣ ብዙ የአካባቢው ነዋሪዎችም ምስሎቹን ያስታውሳሉ።

ከዚህም በላይ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ፣ እንደ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ጊውዴካ ደሴት በሚገኘው የሴቶች እስር ቤት ውስጥ ተገኝተው መስዋዕተ ቅዳሴን ያሳረጉ ሲሆን በነዲክቶስ 16ኛ እዚያ በነበሩበት ወቅት በተመሳሳይ መልኩ ለአርቲስቶች ንግግር አድርገው እንደ ነበረ ይታወሳል።

 

29 April 2024, 14:28