ፈልግ

Cookie Policy
The portal Vatican News uses technical or similar cookies to make navigation easier and guarantee the use of the services. Furthermore, technical and analysis cookies from third parties may be used. If you want to know more click here. By closing this banner you consent to the use of cookies.
I AGREE
የማታ ጸሎት በላቲን ቋንቋ
መርዐ-ግብር በድምጽ የቀረበ ዘገባ

ር.ሊ.ጳ ፍራንችስኮስ ልባችንን ለኢየሱስ ብርሃን እንክፈት ማለታቸው ተገለጸ!

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ዘወትር እሁድ በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለሚሰበሰቡ ምዕመናን በለቱ በሚነበበው የቅዱስ ወንጌል ክፍል ላይ ተንተርሰው አስተንትኖ እንደሚያደርጉ ይታወቃል። በእዚህ መሰረት ቅዱስነታቸው በየካቲት 17/2016 ዓ.ም የጎርጎሮሳዊያኑን የቀን አቆጣጠር በሚከተሉ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ምዕመናን ዘንድ በተጀመረው የሁለተኛው የዐብይ ጾም ሳምንት ላይ ከማርቆስ ወንጌል ተወስዶ በተነበበውና “ከስድስት ቀን በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን አስከትሎ ወደ አንድ ረዥም ተራራ ይዟቸው ወጣ፤ ብቻቸውንም ነበሩ፤ በፊታቸውም ተለወጠ፤ ልብሱም በምድር ላይ ማንም ዐጣቢ ዐጥቦ ሊያነጣው በማይችልበት ሁናቴ እጅግ ነጭ ሆነ። ኤልያስና ሙሴም ከኢየሱስ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው።

ጴጥሮስም ኢየሱስን፣ “መምህር ሆይ፣ እዚህ ብንኖር ለእኛ መልካም ነው፤ አንድ ለአንተ፣ አንድ ለሙሴ፣ አንድ ለኤልያስ የሚሆኑ ሦስት ዳሶች እንሥራ” አለው። እጅግ ስለ ፈሩ የሚናገረውን አያውቅም ነበር።

ከዚያም ደመና መጥቶ ጋረዳቸው፤ ከደመናውም ውስጥ፣ “ይህ የምወድደው ልጄ ነው፤ እርሱን ስሙት!” የሚል ድምፅ መጣ። ወዲያውም ዙሪያቸውን ሲመለከቱ ከኢየሱስ በቀር ማንም አብሯቸው አልነበረም።

ከተራራው ላይ በሚወርዱበትም ጊዜ፣ የሰው ልጅ ከሙታን እስኪነሣ ድረስ ያዩትን ለማንም እንዳይናገሩ አዘዛቸው” በሚለው የቅዱስ ወንጌል ክፍል ላይ ተንተርሰው ባደረጉት አስተንትኖ ልባችንን ለኢየሱስ ብርሃን ልንከፍት ይገባል ማለታቸው ተገልጿል።

የእዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ ቫቲካን

ክቡራን እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ተከታታዮች ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ በወቅቱ ያደረጉትን አስተንትኖ ሙሉ ይዘቱን እንደሚከተለው አሰናድተነዋል፣ ተከታተሉን።

የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ እንደምን አረፈዳችሁ!

በዛሬው እለት በተጀመረው ሁለተኛው የዐብይ ጾም እለተ ሰንበት ላይ የተነበበው ቅዱስ ወንጌል ታምራዊ በሆነ መልኩ የኢየሱስ መልክ መቀየሩን የሚገልጽ ታሪካ ያቀርብልናል (ማር. 9፡2-10)።

ኢየሱስ ተላልፎ እንደሚሰጥ፣ እንደሚካድ እና ብዙ ፈተና እንደሚደርስበት የሚገልጸውን ሕማማቱን ለደቀ መዛሙርቱ ከተናገረ በኋላ፣ ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን ይዞ ወደ ረጅም ተራራ ወጣ፣ እናም በዚያ በአካል በሙሉ በብርሃኑ ተገለጠ። በዚህ መንገድ እስከዚያች ቅጽበት ድረስ አብሮ ከነርሱ ጋር የነበረበትን ትርጉም ገልጾላቸዋል። ስለመንግሥቱ ያደረገው ስብከት፣ የኃጢአት ሥርዬት፣ ፈውሶች እና የተደረጉት ምልክቶች፣ በእርግጥም ከበለጠ የብርሃን ፍንጣሪዎች ማለትም የኢየሱስ ብርሃን፣ ኢየሱስ የሆነው የብርሃን ፍንጣሪዎች ነበሩ። እናም ከዚህ ብርሃን፣ ደቀመዛሙርቱ በተለይ በፈተና ጊዜ፣ ልክ በዚህ ጊዜ በህማማቱ ወቅት እንደተከሰተው ዓይኖቻቸውን ቀና አድረገው መመልከት አልቻሉም።

ይህ የዛሬ መልእክት ነው፣ አይኖችህን ከኢየሱስ ብርሃን ፈጽሞ አትንቀል። ቀደም ባሉት ጊዜያት ገበሬዎች እርሻቸውን ሲያርሱ ይሠሩት እንደነበረው ማለት ነው፡ ከፊታቸው ባለው ልዩ ነጥብ ላይ አተኩረው ዓይኖቻቸውን እዚያው ላይ እያደረጉ መቆፈራቸውን ይቀጥላሉ።

በሕይወታችን ውስጥ በምንጓዝበት ጊዜ እንደ ክርስቲያን ልናደርገው የተጠራነው ይህንን ነው፡ የኢየሱስን አንጸባራቂ ፊት ሁልጊዜ በዓይኖቻችን ፊት እንድናይ።

ወንድሞች እና እህቶች፣ የኢየሱስን ብርሃን ለመቀበል ልባችን ክፍት ይሁን! እርሱ ፍቅር ነው፣ እርሱ ፍጻሜ የሌለው ሕይወት ነው። ከጊዜ ወደ ጊዜ ሊያሰቃዩ በሚችሉ የሕይወት መንገዶች ላይ፣ በምህረት፣ በታማኝነት እና በተስፋ የተሞላ ፊቱን እንፈልግ። ይህንን ለማድረግ የሚረዳን ጸሎት፣ ቃሉንና ምስጢራትን በተለይም ምስጢረ ንስሐ እና ቅዱስ ቁርባንን ስናዘወትር፣ እርሱን ለማዳመጥ፣ ወደ እርሱ ለመጸለይ፣ ቃሉን እና ምስጢራትን ማዳመጥ ዓይኖቻችንን በኢየሱስ ላይ እንድናተኩር ይረዳናል።

ይህ ደግሞ ጥሩ የዐብይ ጾም ውሳኔ ነው፡ እንግዳ ተቀባይ አመለካከትን ማዳበር፣ "ብርሃንን ፈላጊዎች" መሆን፣ የኢየሱስን ብርሃን ፈላጊዎች በመሆን፣ በጸሎትም ሆነ በሰዎች ውስጥ የኢየሱስን ብርሃን ልንፈልግ ይገባል።

እንግዲያውስ ራሳችንን እንጠይቅ፡- አይኖቼ ከእኔ ጋር ሊጓዝ ወደሚመጣው ክርስቶስ ላይ ያተኩራሉ ወይ? እናም ይህን ለማድረግ ለዝምታ፣ ለጸሎት፣ ለስግደት ቦታ እሰጣለሁ ወይ? በመጨረሻም፣ በእኔ እና ባጋጠሙኝ ወንድሞችና እህቶች ውስጥ የሚንፀባረቀውን የኢየሱስን ትንሽ ጨረሮች እሻለሁ ወይ? እናም ለዚህም እሱን ማመስገን ትዝ ይለኛል ወይ?

በእግዚአብሔር ብርሃን የምትበራ ማርያም ይናችን በኢየሱስ ላይ እንዲያተኩር እና እርስ በርሳችን በመተማመን እና በፍቅር እንድንተያይ እርሷ በአማላጅነቷ ትርዳን።

26 Feb 2024, 09:53

መልኣኩ ገብርኤል ማሪያምን አበሰራት የሚለው የቀርብ ጊዜ ጸሎት

ሁሉንም ያንብቡ >
Prev
February 2025
SuMoTuWeThFrSa
      1
2345678
9101112131415
16171819202122
232425262728 
Next
March 2025
SuMoTuWeThFrSa
      1
2345678
9101112131415
16171819202122
23242526272829
3031